ሐሙስ 27 ኦገስት 2026 ጥዋት 9:45:37
ከዕፅ ጋር በተያያዙ ጥፋቶች የሚፈረደቸባው ሰዎችን በሞት እየቀጣች ባለችው ሳዑዲ አረቢያ ውስጥ፣ በነሐሴ ወር ብቻ ጫትን ጨምሮ የተለያዩ ዕፆችን በማጓጓዝ የተጠረጠሩ ቢያንስ 60 ኢትዮጵያውያን በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ዘገባዎች አመለከቱ። ትናንት ረቡዕ ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም. ተጨማሪ 15 ኢትዮጵያውያን ከ290 ኪሎ ግራም ጫት ጋር መያዛቸው ተዘግቧል።
__
የዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ከሳዑዲ አረቢያ ጋር የተደረሰውን የሰላማዊ ኒውክሌር ትብብር ስምምነት እንዲገመገም ለአሜሪካ ኮንግረስ አስተላለፈ። በዚህም አገሪቱ ከሳዑዲ ጋር የተፈራረመችው የኒውክሌር ስምምነት በአሜሪካ የአውቶሚክ ኢነርጂ ሕግ መሠረት የሚገመገምበት ሂደት እንዲጀመር ያደርጋል።
ረቡዕ 26 ኦገስት 2026 ከሰዓት 3:19:19
የአፍሪካ ኅብረት ፌደራል መንግሥት እና የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) አመራሮችን ለማሸማገል የሚያደርገውን ጥረት እንደሚደግፉ የአውሮፓ ኅብረት አባል የሆኑ የ22 አገራት እንዲሁም የዩናይትድ ኪንግደም፣ ኖርዌይ እና ካናዳ ኤምባሲዎች አስታወቁ። አገራቱ፣ "ክፉኛ በድርቅ በተጎዳው" ትግራይ ክልል የሚጀመር ወታደራዊ ግጭት ለሰሜን ኢትዮጵያ ሕዝብ "አስከፊ" እንደሚሆን አስጠንቅቀዋል።
ረቡዕ 26 ኦገስት 2026 ጥዋት 9:43:43
በአገራዊ ምክክሩ ላይ ከተሳተፉ የፖለቲካ ፓርቲዎች አንዱ የሆነው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)፣ በቀጣይ የምክክር ሂደቱ ምዕራፎች መተግበር አለባቸው ያላቸውን አምስት ማሳሰቢያዎች ይፋ አደረገ። ኢዜማ፣ ዛሬ ረቡዕ ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም በሰጠው መግለጫ ተመካካሪዎች በሙሉ ድጋፍ ያልፈረሙባቸውን ምክረ-ሐሳቦች እንደማይቀበል ጨምሮ አስታውቋል። 4000 ተመካካሪዎችን አሳትፎ ከሐምሌ 8 ጀምሮ ከአንድ ወር በላይ የተካሔደው እና በርካታ ጥያቄዎች የተነሱበት የምክክር ሂደት ቅዳሜ ነሐሴ 16/2018 ዓ.ም. በተካሔደ የመዝጊያ ሥነ ሥርዓት ተጠናቅቋል።
ማክሰኞ 25 ኦገስት 2026 ጥዋት 5:05:13
በጁባ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ የደቡብ ሱዳን ባለሥልጣናት ሁለት የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ወታደሮች ስለተገደሉበት ጥቃት ምርመራ እንዲደረጉ ጠየቀ። የተባበሩት መንግሥታት የደቡብ ሱዳን ተልዕኮ ባወጣው መግለጫ፣ በተፈጸመው "ደፈጣ ጥቃት" ሰላም ማስከበር ላይ የተሰማሩ ሁለት ኢትዮጵያውያን ወታደሮች ሲገደሉ ሰባት ሰዎች እንደቆሰሉ አስታውቋል።
ማክሰኞ 25 ኦገስት 2026 ጥዋት 8:08:43
ከፕሪቶሪያ ስምምነት አደራዳሪዎች አንዱ የሆኑት የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ ትናንት ሰኞ በትግራይ "በድንገተኛ ጉብኝት" ማድረጋቸውን ህወሓት የሚመራው የክልሉ አስተዳደር አስታወቀ። ህወሓት መሩ አስተዳደር ከፌደራል መንግሥት ጋር ውይይት ለመጀመር "መሠረታዊ እና ቁልፍ" ናቸው ያላቸውን ቅድመ ሁኔታዎች አስቀምጧል።
ዓርብ 21 ኦገስት 2026 ጥዋት 10:30:59
ወደ ማጠናቀቂያው በተቃረበው የአገራዊ ምክክር ጉባኤ ላይ የአዲስ አበባ ጉዳይ መግባባት ያልተደረሰበት እና ሂደቱን ያዘገየ አጀንዳ ሆኗል። ሐሙስ ዕለት በተካሄደው ጉባኤ ላይ አዲስ አበባን በተመለከተ ክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች ስለተነሱት ምክረ ሀሳቦች ምንጮች ለቢቢሲ ተናግረዋል። የኦሮሚያ እና አማራ ክልሎች አመራሮች መካከል በመዲናዋ ጉዳይ ልዩነት መታየቱንም ተሳታፊዎቹ ገልጸዋል።
ሐሙስ 20 ኦገስት 2026 ጥዋት 10:06:03
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሁለት ዓመት ሊሞላው ወራት በቀረው የሁለተኛው የሥልጣን ዘመናቸው፣ ስደተኞች እና ጥገኝነት ጠያቂዎችን ዒላማ ያደረጉ ትዕዛዞችን አሳልፈዋል። በተለያየ መንገድ ኢትዮጵያውያን ላይ ጫና ሊያሳድሩ የሚችሉ የትራምፕ አስተዳደር አራት ውሳኔዎችን እንመልከት።
ሐሙስ 20 ኦገስት 2026 ጥዋት 4:01:34
የግብፅ መንግሥት፣ በአገሪቱ የሚገነባው 'ኤል ዳባ' የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ማብላያዎች (ሪአክተር) ላይ "ጉድለት" እንደተገኘ በመግለፅ ግንባታውን የሚያከናውነው የሩሲያው ኩባንያ ላይ አቅርቦታል የተባለው ወቀሳ ውዝግብ አስነስቷል። “የኒውክሌር ደኅንነት አሠራር" ላይ ጥሰት ስለመፈጸሙ የወጣውን ዘገባ ተከትሎ ምላሽ የሰጡት የግብፅ ባለሥልጣናት፣ ጉዳዩን አስተባብለዋል።
ቅዳሜ 22 ኦገስት 2026 ጥዋት 10:22:16
በኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ጉባኤ ሲከራክር በቆየው የአዲስ አበባ ጉዳይ ላይ የከተማዋ "የኦሮሚያ ክልል መቀመጫነት በፌደራል ሕግ መንግሥት እንዲሰፍር" የሚጠይቅ ምክረ ሃሳብ መቅረቡን ምንጮች ለቢቢሲ ተናገሩ። ከተማዋ "ከኦሮሚያ ክልል ጋር የሚኖራትን ግንኙነት" በተመለከተ ግን ኮሚሽኑ የመጨረሻውን የሚለው ምክረ ሀሳብ ለመንግሥት እንደሚያቀርብ ማስታወቁን አንድ ምንጭ ገልጸዋል።
ማክሰኞ 18 ኦገስት 2026 ከሰዓት 1:39:56
በሀገራዊው ምክክር ላይ የድሬዳዋ ከተማ በፌዴራል ከተሞች ጉዳይ ስር ምክክር ከተደረገባቸው ሁለት ከተሞች አንዱ ነው። ከኦሮሚያ እና ከሶማሌ ክልሎች በተወከሉ የምክክሩ አባላት መካከል ከፍተኛ የይገባኛል ክርክር እንደተደረገባት በምክክሩ ላይ የተሳተፉ ታማኝ ምንጭ ለቢቢሲ ተናግረዋል። ይሁን እንጂ የአዲስ አበባ ከተማ ጉዳይ ሰፊ መነጋገሪያ መሆኑ፣ የድሬዳዋ ጉዳይ ብዙም ትኩረት እንዳያገኝ አድርጎታል። ለመሆኑ በድሬዳዋ ላይ ምን ዓይነት ስምምነት ተደረሰ?
ሐሙስ 13 ኦገስት 2026 ጥዋት 7:53:01
አንድ ወር ባስቆጠረው አገራዊ ምክክር ስምንት አጀንዳዎች ላይ ሲመክሩ የቆዩት ከአራት ሺህ በላይ ተሳታፊዎች ወደ መቋጫው እየተቃረቡ ነው። በዚህ ሂደት የአዲስ አበባ ጉዳይ ከሌሎች አጀንዳዎች በበለጠ አነጋጋሪ እና ስምምነት ላይ ለመድረስ አዳጋች ሆኖ ታይቷል። በአዲስ አበባ የምክክር አጀንዳ ላይ የተከሰተው ምንድን ነው? ያላግባቡት ጉዳዮችስ የትኞቹ ናቸው?
ሰኞ 10 ኦገስት 2026 ጥዋት 4:05:08
ከጋብቻ በፊት የሚደረገው የሽምግልና ሥነ ሥርዓት ከፍተኛ ድግስ እና ገንዘብ የሚፈስበት እየሆነ መጥቷል። ከሚዘጋጀው ድል ያለ ድግስ ባሻገር በመቶ ሺዎች ብር የሚያስወጡ ቄንጠኛ ግዙፍ የአበባ ‘እቅፎች’ ደግሞ የሽምግልናው ሥርዓት አካል ሆነዋል። በተለይ የሚቀርበው የአበባ ስጦታ መነጋገሪያ ሆኗል። የሽምግልና ሥነ ሥርዓት የሰርግን ቦታ እየተካ ነው? ግዙፉ የአበባ ስጦታስ ከየት የመጣ ልማድ ነው?
እሑድ 16 ኦገስት 2026 ጥዋት 6:40:52
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን)፣ በሀገራዊ ምክክር ሂደት ላይ "ከተራ የአሠራር ግድፈት" የዘለሉ "ተደጋጋሚ እና የተደራጁ ጥፋቶች ተፈጽመዋል" ሲል ከሰሰ። "ገዢው አካል መዋቅራዊ ጥሰቶችን" እንደፈጸመ በማንሳት የከሰሰው አብን፣ በአዲስ አበባ ጉዳይ ላይ "የከተማዋ ነዋሪዎች ድምፅ እና ፍላጎት በአግባቡ ሳይወከል" መታለፉን ገልጿል። በሂደቱ ላይ የተፈጸሙት "ተደጋጋሚ እና የተደራጁ ጥፋቶች" የሀገራዊ ምክክሩን "ተዓማኒነት፣ አካታችነት፣ ገለልተኝነት እና ፍትሐዊነት ጥያቄ ውስጥ የሚስገቡ" እንደሆኑም ገልጿል።
ረቡዕ 12 ኦገስት 2026 ጥዋት 6:44:29
በአማራ ክልል ከተከሰተው ቀውስ ጋር በተያያዘ በሽብር ለተከሰሱት ከሦስት መቶ በላይ ፖለቲከኞች፣ ጋዜጠኞች እና ሌሎች ግለሰቦች በይቅርታ እንዲለቀቁ ሂደት ላይ ይገኛሉ። ለሽብር ተከሳሾች የቀረበው የይቅርታ ሰነድ በክልሉ ለተፈፀሙ ግድያዎች እና ጉዳቶች ተከሳሾቹ ኃላፊነት እንዲወስዱ የሚጠይቅ መሆኑን ቢቢሲ የተመለከተው ሰነድ ያሳያል።
ረቡዕ 12 ኦገስት 2026 ከሰዓት 3:28:51
በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ መተከል ዞን በታጣቂዎች በተፈፀመ ጥቃት በርካታ ሰዎች መገደላቸውን እና መቁሰላቸውን ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናገሩ። ጥቃቱ የተፈፀመው ማክሰኞ ነሐሴ 6/ 2018 ዓ. ም. ጠዋት 12 ሰዓት ላይ በዞኑ ዋና ከተማ ግልገል በለስ በሚገኙ ቤተ ክርስቲያናት እና መናኸሪያ ላይ መሆኑን ነዋሪዎች ተናግረዋል።
ሰኞ 3 ኦገስት 2026 ጥዋት 4:02:31
በአማራ ክልል ላለፉት ሦስት ዓመታት በፋኖ ኃይሎች እና በመንግሥት መካከል የሚካሄደው ግጭት የበርካቶችን ሕይወት ቀጥፏል፤ ከፍተኛ ሰብኣዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ውድመትም አድርሷል። ቢቢሲ አማርኛ ያነጋገራቸው የክልሉ ነዋሪዎች ከፍርድ ውጭ ግድያዎችን ጨምሮ ንጹኃን እስር እና እንግልትን እያስተናገዱ መሆኑን ይናገራሉ። የትጥቅ ግጭቶችን የሚመዘግበው አክሌድ ከጥር እስከ ሐምሌ 2018 ዓ.ም. ድረስ ባለው ጊዜውስት ብቻ ከስምንት ሚሊዮን በላይ ሰዎች 'ለግጭት' ተጋልጠዋል ብሏል። ቢቢሲ በግጭቱ በቀጥታ የተጎዱ ነዋሪዎችን እንዲሁም ባለሙያዎችን አነጋግሮ ቀጣዩን ዘገባ አሰናድቷል።
ቅዳሜ 8 ኦገስት 2026 ጥዋት 4:43:37
የሥዕል እና የቅርጻ ቅርጽ ባለሙያ የሆነው ዮናስ መኳንንት፤ ተወልዶ ያደገባትን፣ የእንጀራ ገመዱ የነበረችውን አዲስ አበባን ጥሎ ገጠር ከገባ ከጥቂት ወራት በኋላ ሁለት ዓመት ይሞላዋል። "እኔ እዚህ ከመጣሁ ትልቅ እረፍት ነው የሚሰማኝ። በጣም ሰላማዊ ቦታ ነው፤ ምንም ዓይነት የመኪና ድምጽ የለም፣ የምትሰማው የእንስሳት ድምጽ ብቻ ነው" ይላል።
ሐሙስ 6 ኦገስት 2026 ጥዋት 10:23:36
ከሦስት ዓመት በፊት በትግራይ ክልል መቀለ ከተማ በአሰቃቂ ሁኔታ በተገደለችው ዘውዱ ሃፍቱ ግድያ ተጠርጥረው የዕድሜ ልክ ጽኑ እስራት ተላልፎባቸው የነበሩት ሁለት ፍርደኞች በነጻ እንዲሰናበቱ ተወስኗል። ውሳኔው በሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ዘንድ ከፍተኛ ነቀፌታ ገጥሞታል። በማኅበራዊ ሚዲያ ላይም ቁጣቸውን ገልጸዋል።
ዓርብ 31 ጁላይ 2026 ጥዋት 3:45:20
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ወደ ሥልጣን ከተመለሱ እና ግዙፉን የአሜሪካ የእርዳታ ድርጅት ካፈረሱ በኋላ ለአፍሪካ አገራት የምትሰጠውን ድጋፍ አካሄድ ቀይራለች። ለዚህ ደግሞ ተቃውሞ እና ጥያቄ ያስነሳው ኢትዮጵያን ጨምሮ ከበርካታ የአፍሪካ አገራት ጋር የተፈራረመችው የጤና መረጃ ስምምነት ተጠቃሽ ነው።
ማክሰኞ 18 ኦገስት 2026 ጥዋት 4:03:51
ቱርክ፣ ሳዑዲ አረቢያ እና ፓኪስታን 'የመካ ስምምነት'ን ከፈረሙ ከአንድ ሳምንት በላይ ሆኗቸዋል። አንዳንድ ተንታኞች አገራቱ የተፈራረሙትን የመከላከያ ስምምነት "የሱኒ ስምምነት" ወይም "የሙስሊም ኔቶ" ሲሉ ጠርተውታል።
ሰኞ 29 ጁን 2026 ጥዋት 3:58:53
የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ከአሜሪካ እና ከእስራኤል ጋር ባላት ግንኙነት የተነሳ የኢራን ዋነኛ ዒላማ ከሆነች በኋላ በቀጣናው አገራት ላይ ያላት መተማመን እየቀነሰች ነው። ለፖለቲካ፣ ለምጣኔ ሃብት እና ሌሎች ፍላጎቷን ለማሟላት ከቀጣናው ውጭ መመልከትን መርጣለች። ለዚህም ከሕንድ፣ ከዩክሬን፣ ከግሪክ፣ ከቆጵሮስ እና ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ትስስር እያጠናከረች ነው።
ሐሙስ 14 ሜይ 2026 ጥዋት 4:02:03
ፕሬዝዳንት ትራምፕ የኢራንን ባሕር ኃይል እንዳወደሙ ቢናገሩም፣ ኢራን ትናንሽ ፈጣን ጀልባዎችን በመጠቀም በሆርሙዝ ወሽመጥ የመርከቦችን እንቅስቃሴን መግታት ችላለች። ስለእነዚህ ውጤታማ የኢራን ፈጣን ወታደራዊ ጀልባዎች ምን እናውያለን?
ረቡዕ 8 ኤፕሪል 2026 ጥዋት 4:01:04
ኢራን በአሜሪካ እና በእስራኤል እየተፈጸመባት ባለው ጥቃት ከጠቅላይ መሪዋ ከአያቶላህ አሊ ኻሜኒ ጀምሮ በርካታ ቁልፍ ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ መሪዎቿ ተገድለውባታል። ነገር ግን አመራሯ ሳይፈረካከስ እየተተካካ ፍልሚያውን ቀጥሏል። ለመሆኑ የኢራን አመራር በዚህ ጦርነት ውስጥ ባለበት ጸንቶ እንዴት ሊቀጥል ቻለ?
ረቡዕ 11 ማርች 2026 ጥዋት 12:00:00
አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ ጥቃት መክፈታቸውን ተከትሎ በመካከለኛው ምሥራቅ ውስጥ ጦርነት እየተካሄደ ነው። ኢራን እየተፈጸመባት ላለው ጥቃት አጸፋውን በቀጣናው ባሉ የአሜሪካ ወዳጅ አገራት ላይ እየፈጸመች ነው። ለዚህ ደግሞ ኢራን ርካሽ እና ውጤታማ የሆኑትን ሻሂድ-136 የተባሉ አጥፍቶ ጠፊ ድሮኖችን በስፋት እየተጠቀመች ነው። ይህ በምሥል እና በቪዲዮ የተደገፈው ዘገባ ስለድሮኖቹ ምንነት ይተነትናል።
ማክሰኞ 24 ማርች 2026 ጥዋት 4:02:11
ኢራን በሕንድ ውቅያኖስ ዲያጎ ጋርሲያ ደሴት ላይ ወደሚገኘው የዩናይትድ ኪንግደም (ዩኬ) እና የአሜሪካ የጋራ ወታደራዊ ሰፈር ላይ የረዥም ርቀት ባለስቲክ ሚሳዔሎችን ማስወንጨፏ በመካከለኛው ምሥራቅ ያለውን ግጭት እየተባባሰ መምጣቱን ያሳያል። በእርግጥ ሚሳዔሎቹ ወደታቀደላቸው ዒላማ ሳይደርሱ ቀርተዋል። ነገር ግን የእስራኤል የመከላከያ ሠራዊት ጦርነቱ ከተጀመረ ወዲህ እንዲህ ዓይነት የረዥም ርቀት ሚሳዔሎች ጥቅም ላይ ሲውሉ ይህ የመጀመሪያው እንደሆነ ተናግሯል።
ሰኞ 16 ማርች 2026 ጥዋት 4:02:13
ወታደራዊ ጥቃት የመፈጸም ኃይልን የተመለከቱ ውይይቶች በሚነሱባቸው ወቅቶች አሜሪካ እና እስራኤል እንዴት ኢራንን እያጠቁ እንደሆነ በምሥል ጭምር ከማሳየት ወደ ኋላ አይሉም። በባለሙያ የተዘጋጁ ፎቶዎች እና ቪዲዮዎችን የሚጠቀመው የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ፤ ጥቅም ላይ እየዋሉ ያሉ የመሣሪያ፣ የጄት እና የመርከብ ዓይነቶችን የሚያሳዩ ልጥፎችን በየአጭር ሰዓት ልዩነት ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ይለጥፋል።
ሰኞ 17 ኦገስት 2026 ጥዋት 3:57:58
አይጦች በጎ ስም የላቸውም፤ ሰዎች ከቤታቸው፣ ምግብ እና የተለያዩ እቃዎች ከሚያስቀምጡባቸው ሥፍራዎች አይጦችን ለማራቅ መርዝ ወይም መጥመድ ይጠቀማሉ። በአጠቃላይ አይጦች ከጥፋት ጋር ስለሚያያዙ በበርካቶች ዘንድ የተጠሉ ናቸው። ኢትዮጵያዊው ሳይንቲስት ምርምር የሚያደርጉባቸው ባለ ፓስፖርት አይጦች ግን ለሰው ልጅ ጤና እና ደኅንነት ከፍተኛ ጥቅም አላቸው።
እሑድ 9 ኦገስት 2026 ጥዋት 4:57:37
የአዳም ረታ አዲሱ 'መዝሙረ ሄላም' የተሰኘው የረዥም ልብ ወለድ መጽሐፍ 1,008 ገጾች ሲኖሩት በአምስት ክፍሎች የተከፈለ ነው። ይህ የአዳም አዲስ መጽሐፍ ከዚህ ቀደም የሚጠቀማቸው እንደ ሕፅናዊነት ያሉ ሥነ ጽሑፋዊ ቴክኒኮችን የያዘ መሆኑን በመጽሐፉ አርትኦት ላይ የተሳተፈው ቢኒያም አቡራ ለቢቢሲ ተናግሯል። የመጽሐፉ መቼት ከዚህ ቀደም እንደነበሩ የደራሲው ሥራዎች ከ1950ዎቹ ማለቂያ እስከ 70ዎቹ መጨረሻ ያሉ ናቸው። መጽሐፉ መጠሪያ የሆነችው ሄላም ከዋና ገጸባሕሪያቱ አንዷ ስትሆን በሁሉም ክፍል ውስጥ ትገኛለች። ለሕፅናዊነት አጻጻፉ ኹነኛ ማስተሳሰሪያ በመሆን ታገለግላለች። ቢቢሲ ከአርታኢው ቢኒያም ጋር ያደረገውን ቆይታ እነሆ. . .
ቅዳሜ 1 ኦገስት 2026 ጥዋት 4:56:42
ዲጄ ሲባል መጀመሪያ የሚመጣልን ምሥል ምናልባትም የዳንስ ወለል ላይ ወዝ ወዝ የሚሉ ሰዎች እና ብልጭ ድርግም የሚል መብራት ይሆናል። እነዚህ ዲጄዎች ግን ማንኛውንም ቦታ ለሙዚቃቸው መዳረሻ ማድረግ የሚችሉ ናቸው። ጋራዥ፣ ቴአትር ቤት፣ ፀጉር ቤት፣ መጻሕፍት መደብር፣ ልብስ ሰፊ ቤት፣ ግንባታው ያልተጠናቀቀ 40/60፣ ሸክላ ሠሪ ቤት፣ ወፍጮ ቤት፣ ውይይት ታክሲ. . . የማይገቡበት የለም።
ሰኞ 20 ጁላይ 2026 ጥዋት 3:52:10
ባለፈው ዓመት በሕንድ በዚህ አንጎልን በሚያጠቃ ጥገኛ ተህዋስ የተያዙ ከ200 በላይ ሰዎች ተመዝገበዋል። ይህ ቁጥር በዓለም በአንድ አገር የተመዘገበው ከፍተኛው ሲሆን ከቅርብ ወራት ወዲህ በአገሪቱ እንዲህ ዓይነት ኬዞች መታየታቸውን ቀጥለዋል። ከዚህ በፊት በዓለም አቀፍ ደረጃ የተመዘገቡ የበሽታው ክስተቶች ከ500 ያነሱ ነበሩ።
ቅዳሜ 6 ጁን 2026 ጥዋት 4:22:46
በሰው ሰራሽ አስተውሎት (ኤአይ) ተገርበው በአዲስ መልክ የተሠሩ ሙዚቃዎች የዩቲዩብ ገፆችን ወርረዋል። የአንጋፋ እና ተወዳጅ ድምጻውያን የሙዚቃ ሥራዎች አማርኛው በተኮላተፈ የኤአይ አንደበት እየተዘፈኑ ነው። አንዳንዶቹ በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ ዕይታዎች አሏቸው። የአድማጭን ትኩረት የሳቡም ይመስላሉ። ለመሆኑ የዘመኑ የቴክኖሎጂ ልህቀት በተለይ በሙዚቃው ዘርፍ ምን ያሳጣ፣ ምን ያስገኝ ይሆን? የኢትዮጵያን ሙዚቃስ በምን መልኩ ሊለውጠው ይችላል?
ማክሰኞ 28 ጁላይ 2026 ጥዋት 3:59:29
በኢትዮጵያ ከግማሽ በላይ የሚሆኑ ሴቶች ባል ሚስቱን ለመደብደብ አሳማኝ ምክንያት ይኖረዋል ብለው እንደሚያምኑ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ያደረገው ጥናት አመለከተ። ሚስትን ለመምታት አሳማኝ ምክንያት እንዳለ የሚያስቡ ወንዶች ብዛት ከሴቶች ያነሰ ቢሆንም፤ ከዚህ ቀደም ከነበረው አንጻር በ11 በመቶ ጨምሮ ተገኝቷል።
ሰኞ 20 ጁላይ 2026 ጥዋት 3:52:10
ባለፈው ዓመት በሕንድ በዚህ አንጎልን በሚያጠቃ ጥገኛ ተህዋስ የተያዙ ከ200 በላይ ሰዎች ተመዝገበዋል። ይህ ቁጥር በዓለም በአንድ አገር የተመዘገበው ከፍተኛው ሲሆን ከቅርብ ወራት ወዲህ በአገሪቱ እንዲህ ዓይነት ኬዞች መታየታቸውን ቀጥለዋል። ከዚህ በፊት በዓለም አቀፍ ደረጃ የተመዘገቡ የበሽታው ክስተቶች ከ500 ያነሱ ነበሩ።
































